User Manual "የ2017 በጀት አመት  የ12 ወራት የእቅድ አፈፃፀም  የማጠቃለያ ሪፖርት ቀረበ።"

"የ2017 በጀት አመት  የ12 ወራት የእቅድ አፈፃፀም  የማጠቃለያ ሪፖርት ቀረበ።"

16th July, 2025

የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 የበጀት ዓመት የተከታታይ 12 ወራት የዕቅድ አፈጻፀም ሪፖርት በዛሬው ዕለት ሁሉም የኮሌጁ ማኅበረሰብ በተገኘበት አቀረበ::

ሪፖርቱን አቶ ደረሰ ጌታቸው የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዩች ም/ዲን ፣አቶ ግሩም ቃል ዘነበ  የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አገልግሎት አስተባባሪ እና አቶ ወንዱ ለሜሳ የተቋማት ልማት የአቅም ግንባታ ጉዳዩች ም/ዲን አቅርበዋል ።

ወ/ሮ ዘነቡ ዘረአብሩክ የእቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር   እና የ2018እቅድ    አቅርበዋል::

የኮሌጁ ማኅበረሰብ በቀረበው ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት፣ ሐሳብ አስተያየት እና በቀጣዩ በ2018 የበጀት ዓመት ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ያሏቸውን ሐሳቦችን አቅርበዋል::

በቀረበዉ ሀሳብ አስተያየት ጥያቄዎች ላይ አመራሮች ምላሽ ሰጥተዋል ።

የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተስፋዬ አድማሱ "ኮሌጁ በ2017 የበጀት ዓመት አንጋፋነቱን ያስመሰከሩ ሰፊ ስራዎችን ተሰርቷል:: ይሕ ጥንካሬው በከተማ ደረጃ በክሕሎት: በቴክኖሎጂ እና በጥናትና ምርምር ውድድር ቀዳሚ ሆኖ  አጠናቋል" ያሉ ሲሆን ያሉ ክፍተቶችን በመሙላት ለ2018 የበጀት ዓመት ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል::

ዛሬ የቀረበው ሪፖርት በዚህ ደረጃ ከመገምገሙ በፊት በስራ ክፍል ደረጃ ፣ በፕሮሰስ ካውንስሉ እና በጠቅላላ ካውንስል  በሚገባ ተገምግሞ እንደነበር የሚታወስ ነው።

ተግባረ ዕድ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን

ሀምሌ 9/2017/ዓ.ም

.

Copyright © All rights reserved.

Created with